የመላ ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ (መኢሶን) ፀናሽ ቡድን የመጨረሻ ስብሰባ በሰኔ/ሐምሌ 1960 ወይም ከ 02/06/1968 እስከ 02/07/1968 ጀርመን አገር ሃምበርግ በሚባለው ከተማ ለአንድ ወር በየደረጃው ተደረገ።
ቡድኑ በዚህኛው ስብሰባ ላይ ሲወያይ የቆየውም ለመመሥረቻው ጉባዔ በሚቀርቡት ሰነዶችና ስለጉባዔውም አመራር ነበር።
መኢሶን በዚሁ በሃምበርግ ከተማ ሐምሌ 1960 ወይም ከ01/08/68 እስከ 06/08/68 በተካሄደው የመመሥራቻ ጉባዔ ተመሠረተ።
ስለመመሥረቱ የሚያውቁት 17 መሥራች አባሎቹ ሲሆኑ መሥራች ጉባዔው ላይ የተገኙት ግን 25 ነበሩ።